ከዓድዋ ተራሮች እስከ ጉባ፤ የዓድዋ ድል በታላቅ ክብር እየታወሰ ነው - የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት

ከዓድዋ ተራሮች እስከ ጉባ፤ የዓድዋ ድል በታላቅ ክብር እየታወሰ ነው - የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት

የዓድዋ ድል በጦር ሜዳ የተገኘ ድል ብቻ ሳይሆን፣ ኢትዮጵያ የራሷን ዕድል በራሷ የመወሰን አቅሟን ለዓለም ያሳየችበት የታላቅነት ማወጃ ነው።
ዛሬ የምናከብረው የአባቶቻችንን መሥዋዕትነት እና የትላንቱን ድል በማውሳት ብቻ ሳይሆን፣ የዛሬውን አሻራችንን በጽኑ መሠረት ላይ በመገንባት ጭምር እንደሆነ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ገልጿል።
በዓድዋ መንፈስ እየተመራን የሀገራችንን የወደፊት ዕጣ ፈንታ በጋራ መቅረጻችንን እንቀጥላለን። በዓባይ ወንዝ ላይ የተገነባው የኢትዮጵያ ታላቁ የሕዳሴ ግድብ "ሁለተኛው ዓድዋችን" ነው። ይህ ግዙፍ ፕሮጀክት የአሁኑን ዘመን ፍላጎት በመረዳትና ታሪክን በማክበር ለሠራነው ሥራ ሕያው ምስክር ነው።
በመደመር ዕሳቤ ውስጥ የሚገኘው የዓድዋ መንፈስ ሲመራን፣ ሀገራችን የማታሳካው ምንም ዓይነት ግብ የለም። በአንድ ዓላማና በጋራ ስምምነት ስንንቀሳቀስ የኢትዮጵያ አቅም ሊገታ የማይችል ይሆናል። "ትላንት ታላቅ ነበርን፤ ነገ ደግሞ ከትላንቱ ይልቅ በላቀ ሁኔታ ታላቅ እንሆናለን" ሲል የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ገልጿል።


አስተያየትዎን ያጋሩ
ቋንቋ ይቀይሩ
ፍለጋ
ወቅታዊ ዜናዎች
የስራ ማስታወቂያ
SBC
የፌስቡክ ገጽ
ዩቲዩብ